Wednesday, April 24, 2013

በእግዚአብሔር ፍቅር



ከእግዚአብሔር ጋር ከመገናኘት የበለጠ ሕይወትን የሚቀይር ነገር የለም፡፡
እግዚአብሔርን እንደማግኘት ብርቱ የኾነ ነገርም የለም፡፡
ይህም ወደኋላ ላይመለሱ በእግዚአብሔር ፍቅር ተይዞ ወደፊት መጓዝ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ስታፈቅር

ሐሳብኽ እርሱን ከማሰብ አያርፍም፤ 
የምታደርገው ነገር ኹሉም ለእርሱና ስለ እርሱ ብቻ ይኾናሉ፡፡

ጠዋት ከእንቅልፍኽ የምትነሣበት ምክንያትኽ
የምሽት ተግባራትኽ መንሥኤ
የዕረፍት ቀናትኽን የማሳለፊያ መንገድኽ
የምታነብባቸውን መጻሕፍትና የምትተዋወቃቸውን ሰዎች መምረጫ ሚዛንኽ
የሚያሳዝኑኽና የሚያስደንቁኽን ጉዳዮች መስፈሪያኽ
የሚያስደስቱኽና የምትረካባቸውን ነገሮች መለኪያኽ
እርሱ ብቻ ይኾናል፡፡
ፍቅሩን አጥብቀኽ ፈልግ፡፡ ለፍቅሩ ልብኽን ክፈት፡፡ በፍቅሩ ኑር፡፡
ያኔ ሕይወትኽ በፍቅሩ ይለወጣል፡፡ 

(Source:- Javier Uriarte (SJ). Reprinted from: Review of Ignatian Spirituality) 
Special Gratitude to Abba Groum Tesfaye (SJ)

No comments:

Post a Comment