Tuesday, April 3, 2012

አንድምታ (The Ethiopian way of Interpreting the Holy Bible)

ከቀደሙ ኢትዮጵያውያን አበው መካከል ቅዱሳት መጻሕፍትን እጅግ ከማፍቀራቸው የተነሣ ንባቡ አላጠግብ ቢላቸው ወደ ትርጓሜ ዘልቀው፣ በዓለም የነበረውን የቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀት መሠረት አድርገው እነርሱ ራሳቸው በትርጓሜ እየተራቀቁ፣ እየመጠቁ የሚጓዙ አበው ነበሩ፡፡ ከእነዚህ አበው የትርጓሜ ሥራዎች መካከል አንድምታ በመባል የሚታወቀው የትርጓሜ አካሄድ አንዱ ነው፡፡

ምንም እንኳ አንድምታ ምንጩ በልዩ ልዩ ሀገራት የነበሩ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ቢሆኑና ለኢትዮጵያዊው ትርጓሜ እነርሱን መሠረት ቢያደርጉም ኢትዮጵያውያኑ ሊቃውንት እንዲሁ በመዋስ ብቻ ግን አልተወሰኑም፡፡ ይልቁንም እነርሱም ዕውቀታቸው ያራቀቃቸውን፣ እምነታቸው ያመጠቃቸውን ያህል መሠረቱን አስፋፍተውታል፤ አሳድገውታል፤ አምጥቀውታልም፡፡ ሆኖም ይህ የምጥቀት ጉዞው በአንዳንድ ምክንያቶች የተደናቀፈባቸው፣ የጫጨባቸው እንዲሁም የተገደለባቸው አጋጣሚዎችም ነበሩ፡፡ ከእነዚህም መካከል አንዱ ትርጓሜ በየጊዜው እያደገና እየሰፋ የሚሄድ ነገር ሳይሆን እንደጸሎት የሚደገም የማይሻሻልና የማይታረም እንደዶግማ ፍጹም ተደርጎ መቆጠሩ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- እርሳቸው ራሳቸው የትርጓሜ መምህር የነበሩትና ዘመኑን የቀደመ ኢኩሜኒካል አስተሳሰብ የነበራቸው መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ የሚከተለውን ጽፈው ነበር፡-