Saturday, April 26, 2014

I think, the Ethiopian government is allergic to independent thinkers

I am too depressed even to say a word! 

One of my friends is in jail just because he thinks the government is wrong in many aspects. A month ago we were talking about how things are going from bad to worse in our country. 

As the election year is approaching the government of Ethiopia has started to crackdown against any dissident voices. Including those voices of bloggers on facebook who criticize the maladministration in Ethiopia. The famous Zone9 young writers and others like the poet Dawit Tsegaye are now jailed by the government. I wish the regime is as efficient in serving the public as in imprisoning young writers who just want to share their ideas with their fellow citizens.

Some Wh questions to the Ethiopian Government

Why does each and every door of dialogue have to be closed? Why is the government in total opposition with people who want to think independently and critically?

In Ethiopia thinking has become a huge offense against the government which seems to have a disease called Thinking Allergy. 

But here is what they have to know, although they want to stay in power forever, they can't, just because they are human beings. 

Tuesday, April 8, 2014

ዐረፍተ ነገሯ ስትመዘዝ፤ የመብራት ኃይል ጉዳይ (Anayzing the Sentence of the Deputy Prime Minister)

ይኽን ጽሑፍ ከጻፍኹ ትንሽ ቆየት ብሏል፡፡የጻፍኹትም አንድ መጽሔት ውስጥ ያነበብኹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ተብሎ ይጠራ የነበረውን ተቋም ከኹለት መከፈል የሚያትት ዜና ላይ አንድ ሐሳቤን የቆነጠጠችኝ ነገር ከተመለከትኹ በኋላ ነው፡፡
እንደመጽሔቱ ዘገባ ሠራተኞቹም በአዲሱ አወቃቀር ውስጥ ለመካተት እንዲችሉ በእንግሊዘኛ የተዘጋጀ ቅጽ እንዲሞሉ ተጠይቀዋል አሉ፡፡ ይኼ ሲያሻው እጨለማ ውስጥ የሚያሳድረንን፣ ሲያሻው ሥራ አስፈትቶ የሚያውለንን ብልጭ ድርግም የሚያስቀርልን ከኾነ እሰየው! እልልልል! እንኳን እኹለት ለምን ሃያ ኹለት ቦታ አይከፍሉትም!


እኔን የቆነጠጠኝ መከፈሉ ሳይኾን ሠራተኞቹ እንዲሞሉት የታዘዙት ቅጽ በእንግሊዘኛ የተዘጋጀ መኾኑ ነበር፡፡ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረ ጽዮን ጋር ባደረጉት “ውይይት” ላይ ሠራተኞቹ፣ ቅጹ ለምን በእንግሊዘኛ ኾነ የሚል ጥያቄ አንሥተው እንደነበር መጽሔቱ ያትታል፡፡ ሚኒስትሩም፣ “እነርሱ (ሕንዶቹ) ወደ አማርኛ ከሚመጡ እኛ ወደ እንግሊዘኛ ብንኼድ ይቀለናል የሚል ነው፡፡” ማለታቸው እንደተሰማ ይጠቁማል፡፡


መቼም ነገሩን ላይላዩን ላየው ሰው የሚኒስትሩ መልስ ቀላልና ወጪ ቆጣቢ ይመስላል፡፡ ነገር ግን ውስጡን በማኅበራዊ ሥነ ልሳን (Sociolinguistics) ትምህርት፣ በተለይም ደግሞ ከቋንቋ ፖለቲካና ከቋንቋ አመለካከት (language attitude)  አኳያ፣ ስናየው ሚኒስትሩ ተናገሩ የተባለው ዐረፍተ ነገር የያዘው ፍቺ እጅግ ብዙ ኾኖ እናገኘዋለን፡፡

ሥውርና ገሃድ ፖሊሲ


በቋንቋ ፖለቲካ ትምህርት ውስጥ የቋንቋ ፖሊሲዎች ከሚከፈሉባቸው መንገዶች አንዱ ሥውር (Covert)ና ክሡት (Overt) የሚለው ነው፡፡ ክሡት የሚባሉት የቋንቋ ፖሊሲዎች በገሃድ የሚነገሩ፣ በጽሑፍ የሚሠፍሩና በዐዋጅ የሚታወጁ ሲኾኑ ሥውር የሚባሉት ግን በዐዋጅ ያልታወጁ፣ በጽሑፍም ያልሰፈሩ፣ በገሃድም ያልተነገሩ ነገር ግን በልዩ ልዩ መልኮች ተፈጻሚነትን የሚያገኙና በመፈጸምም ህልውናቸውን የሚያረጋግጡልን የቋንቋ ፖሊሲዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ፣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት አማርኛ የፌደራል መንግሥቱ የሥራ ቋንቋ መኾኑን ያውጃል፡፡ ይኽ እንግዲኽ ክሡት የቋንቋ ፖሊሲ ይባላል፡፡ በዚኽ ክሡት ፖሊሲ የተነሣም የትኛውም የፌደራል መሥሪያ ቤት የሚጠቀመው የሥራ ቋንቋ አማርኛ እንዲኾን ይገደዳል፡፡