Wednesday, September 24, 2014

ወደ ናፖሊዮን ሣልሳይ የቀረበ የቅኝ ተገዢነት ጥያቄ



ቀጥሎ የቀረበው ደብዳቤ በ1859/1851

አገው ንጉሤ ከተሰኘው የኢትዮጵያ መስፍን ወደ ፈረንሳይ ንጉሥ ናፖልዮን ሣልሳይ የቀረበ ወደ ናፖሊዮን ሣልሳይ የቀረበ የቅኝ ተገዢነት ጥያቄ ነው፡፡ በግእዝ የተጻፉትን ዐረፍተ ነገሮች ወደ አማርኛ በቅንፍ ተርጉሜላችኋለኹ፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክና በኢትዮጵያ ነገሥታት (የነበሩትንም ያሉትንም ይመለከታል፡፡) ላይ ትንሽ ይቆዝሙ፡፡ 



ተጽሕፈት በሐውዜን አመ 1ኅዳር እምልደተ እግዚእነ በ%80)9 ዓመትበሐሳበ ሮማ፡፡ ወበኢትዮጵያ በ%80)1  ዓመት አመ&4 ለጥቅምት፡፡ (በሮማውያን አቆጣጠር ኅዳር1ቀን 1859፣ በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ደግሞ ጥቅምት 24 ቀን 1851 ዓመተ ምሕረት በሐውዜን ተጻፈች፡፡)

ንጉሠ ነገሥት ሆይ!
ካገሬ ሥራት አስቀድሜ ለጣቃዬ ያክስቴ ልጅ እርሱም ከፈረንሳዊ አገር ሲመለስ መርከብ በመሰበር በባሕር መሞቱ ልቤን የሚያሳዝነኝን ባደረጉለት መልካም ሥራት አመሰግነዎ አለኍ፡፡ 

የእግሊዞች ተንኮል አውለቃኍ፡፡ ቈንስላቸውን ቴዎድሮስ በሉኝ ወደሚል ቋረኛ ካሳ መስደዳቸውን አውቃለኁ፡፡ ክፋታቸው ሳይበዛ በጭንቅ ጊዜ ልቤን ወደርስዎ የፈረንሲስ ንጉሠ ነገሥት አድርጌ አለኍ፡፡ አድርጌም ከእርስዎ የኢጣልያን ዓርነት ጠባቂ በታላቅ ኃይልዎ ያገሬን ዓርነት እንዲጠብቁልኝ የሥራት ብርሃንም ወዳገሬ እንዲያደርሱልኝ ከዘራፊ ከቴዎድሮስ እጅ እንዲጠብቁልኝ እለምነዎ አለኍ፡፡ ይህነንም እንዲፈጸም ሁለት ነገር ያስፈልጋል፡፡ አንዱ በፊት እንደላክሁበዎ ሥራትን ሁሉ የሚያይ የርስዎ ምስለኔ ቢሰዱልኝ ባገሬ እንደራሴ እጠብቃለኍ፡፡ የፈረንሳዊ ባንዴራንም አስተክላለኍ፡፡ ሁለተኛው እኔ የምመኘው እርሱ ነውና ሁለት ባተርያ የመድፍ ከነተኳሽ ጋራ ነው፡፡ ስለሚያደርጉልኝ ነገር ደስ አሰኘዎ አለኊ ብዬ ተስፋ አለኝ፡፡ ስላደረጉልኝና የስዊስን መንገድ ባሕርም በመግጠም ላገሬ ስለሚያደርጉልኝን ራስ ዱማራ የሚባል ዙላን አበረክትዎ አለኍ፡፡
ንጉሠ ነገሥት ሆይ! የነገርሁዎ የልቤን ሐሳብ ቶሎ እንዲፈጽሙልኝ ተስፋ አለኝ፡፡ 


ተወከፍ አምኃተ ትሑታተ እምእኁከ ትሑት ንጉሤ፡፡(ከዝቅተኛ ወንድምኽ ዝቅተኛ ሥጦታዎችን ተቀበል፡፡)


ምንጭ፡- ተስፋዬ አካሉ፡፡ አጤ ቴዎድሮስ በሦስቱ ቀደምት ጸሓፍት፡፡

No comments:

Post a Comment