Monday, September 22, 2014

ፕሮፓጋንዳ የፈጠራት ወያኔ


ኢሕአዴግ ባሕር ዳር የገባ ሰሞን ነው አሉ፡፡ የኢሕአዴግ ሠራዊት ለዕቃ ማጓጓዣነት የሚጠቀምባቸውን ግመሎቹንና አጋሰሶቹን ኹሉ ይዞ ከተማዋን በቁጥጥሩ ሥር እንዳዋላት ግመል አይተው የማያውቁትትንንሽ ልጆች “ወያኔ ያቻት! ወያኔ! ወያኔ ያቻት!” እያሉ ወደ ግመሎቹ ፡፡ ይኼኔ ከሠራዊቱ አባላት አንዱ “ልጆች፣ ይቺ ወያኔ አይደለችም፡፡ ወያኔ እነርሱ ናቸው፡፡” በማለት ጓዶቹን ያሳያቸዋል፡፡ እነርሱም “ወይድ! ልታሞኘን ነው?! እነርሱማ እንደኛ ሰዎች ናቸው፡፡” ብለውት ዕርፍ፡፡ ለካ ወያኔ ማለት ለእነርሱ የኾኑ ታይተው የማያውቁ ፍጥረታት ጭራቆች ነበሩ፡፡ 

አኹን ርእዮት ዓለሙን፣ በቀለ ገርባን ወይም ዞን ዘጠኞችን አይቶ የማያውቅ የኢቲቪ ደንበኛ እኮ “አሸባሪ!” ምናምን ሲባሉ ሲሰማ የኾኑ ፈንጂ ታጥቀው የሚዞሩ ጨካኝ መላእክተ ሳጥናኤል ይመስሉት ይኾናል፡፡ ባለ ራእዩ መሪ ሲባል ደግሞ ብርሃናማ ክንፎች ያሉት፣ ጭንቅላቱ ዙሪያ አክሊለ ብርሃን የተጎናጸፈ፣ ፈገግታው ከሩቅ የሚጣራ ቅዱስ መልአክ ይታየው ይኾናል፡፡ የፕሮፓጋንዳ ጉልበት!የፕሮፓጋንዳ ጉልበት!
 

No comments:

Post a Comment