Friday, September 19, 2014

ግንቦትና ቦረንትቻዎቹ

ሴት አያቴ ጫሊ ወዬቻ ትባላለች፡፡ እውነቴን ነው፡፡ ሐምሌ 24፣ 2002 ዓ.ም. ዐርፋ ቢሾፍቱ መድኃኔዓለም ነው የተቀበረችው፡፡ ነፍሷን ይማርልኝና እጅግ ትወደኝ ነበር፡፡ አንድ ቀን እንዲኽ ጠየቅኋት፡፡ እኔ፡- እማማአያቴ፡- ኦእኔ፡- ቆይ፡ በግንቦት ወር ለምንድነው ሠርግ የማይደረገው? ምን ችግር አለው?አያቴ፡- እንዴት ያለ ጥያቄ ነው ልጄ? በግንቦት ለቦረንትቻ የሚታረድ ከብት እንጂ የልጃጋረድ ደም አይፈስም፡፡ ነዉር ነው!እኔ፡- አሃ! ደግሞ ቦረንትቻ ምንድነው?አያቴ፡- ቦረንትቻ ማለት የደም ግብር የሚገበርለት መንፈስ ነው፡፡ የደም ግብር ካላገቡለት ከብቱን ያጠፋል፤ እኽሉን ያጠፋል፤ ሀብቱን ያጠፋል፡፡
ዛሬ ላይ ቆሜ ይኽን የአያቴን ንግግር ሳስበውና አንዳንድ ሰዎች “ኢትዮጵያ ውስጥ ደም ሳይፈስ ፖለቲካዊ መሻሻል ሊመጣ አይችልም፡፡” ብለው የሚናገሩ ሰዎችን ስሰማ እነዚኽ “ደም ካላፈሰሳችኹልን ወይም ደማችኹን ካላፈሰስን ከሥልጣን አንወርድም፤ ወይም ወደ ሥልጣን አንመጣም፤” የሚሉ ሰዎች ቦረንትቻዎች ናቸው ማለት ነው?” ብዬ አስባለኹ፡፡ “መጠርጠር ደግ ነው!” ይባል የለ? ደግሞ ወሩ ግንቦት መኾኑ! ሆሆ ብዬ ላሽሟጥጥ እንጂ!




No comments:

Post a Comment