Thursday, January 26, 2012

ላምና አሳማ


አንድ ገበሬ አንዲት እርሱና ቤተሰቡ የሚወዷት ላምና አንድ አሳማ ነበሩት፡፡ ለአሳማው ያላቸው ፍቅር ግን የላሚቱን ያህል አይጠናባቸውም ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አሳማው ላሚቷን እንዲህ ይላት ጀመር፡- 
“እንዴት ነው ግን ሰው ሁሉ አንቺን እጅግ አድርጎ ሊወድሽ የቻለው? ሰዎች አንቺ ወተት፣ ቅቤ፣ አይብ ስለምትሰጪ እጅግ ቸር ቸር ናት ይሉሻል፡፡ ኤዲያ! እኔ ከዚያ የበለጠ እሰጥ የለ እንዴ? ሽንጡና ጭቅናው የማን ሆነና ነው? ግን ያንቺን ያህል አልወደድም፡፡ ለምን? ለምን?
ላሚቷም መለሰች፡- “ምናልባት እኔ የምሰጠውን የምሰጠው በሕይወት እያለሁ ስለሆነ ይሆን?

ከሞትን በኋላ የምሰጠው ስጦታ እምብዛም አይደል፡፡ ይልቁንም በሕይወት ሳለን ከሕይወታችን ላይ የምንሰጠው ማለትም በሕይወት እያለን የምናፈቅረው የበለጠ ዋጋ አለው፡፡ 

No comments:

Post a Comment