Wednesday, September 19, 2012

እንደሞተ ሰው


እጅግ ርኅሩኅና መልካም ኢየሱስ ሆይ! እስከ መጨረሻው ሕይወቴ ድረስ ከእኔ ጋር የሚኖረውን፣ በእኔ ውስጥ የሚሠራውንና፣ ከእኔ ጋር የሚቀረውን ጸጋህን ስጠኝ፡፡ እኔ፣ አንተ ዘወትር የምትወደውንና የሚያስደስትህን ነገር ብቻ እንድወድ አድርገኝ፡፡ ያንተ ፈቃድ የእኔ ፈቃድ ይኹን፡፡ የእኔም ፈቃድ ዘወትር የአንተን ፈቃድ ይከተል፤ ፈጽሞም ከእርሱ ጋር ይስማማ፡፡

አንተ ከምትወድደው ነገር በቀር ሌላ እንዳልወድ፤ አንተ ምትጠላው ነገር በቀር ሌላ እንዳልጠላ፤ መውደዴና መጥላቴ ከአንተ ሐሳብ ጋር አንድ እንዲሆን አድርግልኝ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ካሉት ነገሮች ኹሉ እንደሞተ ሰው ተለይቼ እንድኖር አድርገኝ፡፡ ላንተ ፍቅር ስል ራሴን እንድንቅና በዚህ ዓለም መታወቅን እንዳልወድ አድርገኝ፡፡

እኔ ከምመኛቸውና ከምፈልጋቸው ኹሉ በላይ በአንተ ዕረፍት ማግኘትን ስጠኝ፤ ልቡናዬም በአንተ ሰላምን እንዲገኝ አድርግልኝ፡፡ የልቤ እውነተኛ ሰላምና ዕረፍት አንተ ብቻ ነህ፤ ከአንተ ከተለየሁ ግን ኹሉ ነገር ጭንቀትና ሁከት የተሞላበት ይኾናል፡፡

እግዚአብሔር ሆይ! በሰላም እንድኖር የምታደርገኝ አንተ ብቻ ስለኾንህ በምተኛበት ጊዜ በሰላም አንቀላፋለሁ፡፡ (መዝ 4፡ 8)

ምንጭ፡- ክርስቶስን መምሰል

No comments:

Post a Comment