Sunday, May 27, 2012

ከቅዱስ አውጉስጢኖስ ኑዛዜዎች

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሆይ!


ሰማይና ምድርን ትመላለህና እነርሱ ሊይዙህ ይችሉ ይሆን? ወይስ ሊይዙህ ስለማይቻላቸው ሞልተህ ትፈስ ይሆን? ሰማይና ምድርን መልተህ ተትረፍርፈህ ስትፈስስ ወዴት ትፈስ ይሆን? ወይስ ሁሉን የምትይዝ አንተ በርግጥ በምልዐትህ ሁሉን ትይዛለህና በምንም ልትያዝ አትችልም? በምልዐትህ የምትገኝባቸው ሸክላዎች አንተን አይዙህም- ቢሰበሩም እንኳ አንተ አትፈስምና፡፡ በእኛ ላይ ስትፈስም አንተ የምትወርድ አይደለህም- እኛ ወደላይ ከፍከፍ እንላለን እንጂ፡፡ አንተ የምትበተን አይደለህም- እኛን ትሰበስበናለህ እንጂ፡፡ 

Thursday, May 24, 2012

Anima Christi


ይህንን ጸሎት በማስተዋል ያንብቡልኝ፡፡


የክርስቶስ ነፍስ ሆይ! ቀድሰኝ፡፡
የክርስቶስ ሥጋ ሆይ! አድነኝ፡፡
የክርስቶ ደም ሆይ! በሐሴት ሙላኝ፡፡
ከክርስቶስ ጎን የተገኘህ ውኃ ሆይ! እጠበኝ፡፡
ሕማማተ ክርስቶስ ሆይ! አበርታኝ፡፡
መልካሙ ኢየሱስ ሆይ! ስማኝ፡፡
በቁስሎችህም ሸሽገኝ፡፡
ከአንተ ለመለየት ሥቃይ አሳልፈህ አትስጠኝ፡፡
ከክፉው ጠላቴ መከታ ሁነኝ፡፡
በሞቴ ሰዐት ጥራኝ፡፡
ወዳንተ እንድመጣ ጥራኝ፡፡
ከቅዱሳንህ ጋር አንተን ለዘለዓለም እንዳመሰግን፡፡
አሜን፡፡

(ምንጭ፡- Draw me to Your Friendship: The Spiritual Exercises. A Literal Translation and A Contemporary Reading. )

Saturday, May 12, 2012

"God of Surprises" ውብ መጽሐፍ


ሰሞኑን እመለካከታቸው ከነበሩ መጻሕፍት መካከል በአባ ዤራርድ ሒዩስ የተጻፉ ሁለት መጻሕፍት ነበሩ፡፡ አንደኛው “God, where are you?” የሚል ርእስ ያለው ሲሆን ሁለተኛው “God of Surprises” ይሰኛል፡፡ በመጀመሪያው እንደቅዱስ አውጉስጢኖስ ኑዛዜዎች (Confessions) የተባለው መጽሐፍ አባ ዤራርድ ከሦስተ ዓመታቸው ጀምሮ መጽሐፉን እስከጻፉበት ጊዜ ድረስ እግዚአብሔርን ፍለጋ ያደረጉትን ጉዞ ለዛ ባለው ውብ ፍልስፍናዊ ትረካ ያስቃኙናል፡፡ “God of Surprises” የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ የተጻፈበት ዓላማ የመጽሐፉ ጀርባ ላይ እንዲህ ተብሎ ሰፍሯል፡-

Jesus said: ‘The Kingdom of Heaven is like a treasure hidden in a field. This book has only one purpose: to suggest ways of finding the treasure in what we may consider a most unlikely filed- ourselves. It is a guide book to the inner journey which we are all engaged and has much to say to those who have a love/hate relationship with the Church to which they belong or once belonged.  (አጽንዖት የኔ)       

ዐቢይ ጉዳዩ እግዚአብሔር በሕይወታችን የሚሠራባቸውን እኛ ግን የማናስተውላቸውን አስደናቂ መንገዶች በማየትና በዚህም እግዚአብሔር ምን ያህል እንደሚወድደን በማሰብ በፍቅሩ መደነቅ፣ በአሠራሩ ግሩምነት መመሰጥ፣ በሕይወትነቱ መኖር ነው፡፡ ከዚህ መጽሐፍ ካገኘኋቸው ቁም ነገሮች ጥቂቶቹን ላካፍላችሁ፡፡
   
ከእኔ ይልቅ ለእኔ የሚቀርበው እግዚአብሔር

Tuesday, May 1, 2012

ችግር ፈጣሪው ኢየሱስ


በዚህ በሰሙነ ፋሲካ አንድ ጧት የሰውየው በር ተንኳኳኳ፡፡ ሰውየው በሩን ሲከፍት ያየውን ማመን አቃተው፡፡ ኢየሱስ! አዎን ኢየሱስ ከበሩ ላይ ቆሟል፡፡ በድንጋጤ ፈዝዞ ቀረ፡፡ ኢየሱስ ግን “አይዞህ፡፡ አትፍራ፡፡ እኔ ነኝ፡፡” ሲል አረጋጋውና ወደ ውስጥ መዝለቅ ይችል እንደሆነ ጠየቀው ሰውየውም “በደስታ ጌታዬ!” ሲል መለሰለት፡፡ ኢየሱስ ወደ ቤቱ ውስጥ ገባ፡፡ ገና ወንበር ላይ እንኳ አረፍ ሳይል ሰውየው ችግሩን ይዘረዝርለት ገባ- ያደረገውን፣ ማድረግ ያልቻላቸውን፣ ሰዎች ያደረጉበትን፣ በሰዎች የተነሣ በኑሮው ላይ እንዴት ችግር እንደተፈጠረበት፣ ወዘተ.፡፡  ኢየሱስም በፀጥታ ይመለከተው ነበር፡፡ አንዳችም አስተያየት አልሰጠም፡፡ ዝም፡፡
“ጌታዬ እኔ ካንተ ጋር መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እባክህን ሁል ጊዜ ናልኝ፡፡ ከእኔ አትለይ፡፡ እኔ ኮ ብቸኛ ነኝ…”
ችግሩን ዘርዝሮ፣ ዘርዝሮ፣ አልቅሶ፣ አልቅሶ ሲጨርስ ኢየሱስ ከመንገድ እንደመጣ ትዝ አለው፡፡
“ጌታዬ ወንበር ላይ አረፍ በል እንጂ፡፡” ብሎ ወደ ወንበሩ አመለከተውና “ቆይ ሻይ ላፍላ፡፡” ብሎ ወደ ማድቤት ሮጠ፡፡ ሻዩን ይዞ ሲመለስ በር ተንኳኳ፡፡
ኢየሱስም “ኦ! ዘመዶቼ መጡ፡፡ ታስገባቸዋለህ?” ሲል ጠየቀው፡፡
“ጌታዬ ያንተ ዘመዶች መጥተውልኝ? እንዴታ!” የሰውየው መልስ ነበር፡፡ በሩ ላይ ደርሶ እስኪከፍት ድረስ በልቡ ሐዋርያት፣ ሰማዕታት፣ እመቤታችን፣ ቅዱሳን፣ እጣን፣ ደመና፣ መላእክት ወዘተ. እያለ ኼደ፡፡ በሩን ሲከፍት ያያቸው ሰዎች ግን  ቡጭቅጭቅ ያለ ልብስ የለበሱ ወጣቶች፣ ጉስቁል ሕጻናት የታቀፉ የቆሸሹ እናቶች፣ የወገቦቻቸው አለልክ መጉበጥ ደጋፊ ማጣታቸውን የሚመሰክርላቸው ሽማግሌ፣ ወዘተ. ሆኑበት፡፡ አገጩ በድንጋጤ ቁልቁል ወደቀ፡፡ አስገባቸው፡፡ እንዴት እንደሆነ ሊገባው ባይችልም የተፈላው ሻይ ለሁሉም በቃቸው፡፡ ከሻዩ ጋር አብሮ የቀረበው አንድ ሳህን ቆሎም አላለቀም፡፡